MEHARY EDUCATION MINISTRY-Theology for All!

You are not logged in. (Login)

 

Available Courses

  • በዚህ ኮርስ ተማሪዎች የክርስትና እምነት አንኳር የሆኑትን አስተምህሮዎች ይዳስሳሉ።
  • በዚህ ትምህርት ተማሪዎች የክርስትና እምነት ወደ ኢትዮጵያ በእነማን መቼና እንዴት እንደተሰበከ ይማራሉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ታሪክ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንንና የወንጌላዊያን አማኞች አብያተክርስቲያናትን (ፕሮቴስታንት) ጅማሬና ዕድገት እንዲሁም መከራ፣ ስደትና ጽናትን በመዳሰስ አሁን ያሉበትን ሁኔታ ያጠናሉ።
  • በዚህ ኮርስ ተማሪዎች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ የአተረጓጎምን ዘዴ በመጠቀም እንዴት እንደሚተረጉሙና በኑሮአቸውና በአገልግሎታቸው እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚችሉ ይማራሉ።
  • ይህ ኮርስ ከፍጥረት ጅማሬ እስከ ዘመነ መሳፍንት ድረስ ያሉትን አራት የሕግ መጻሕፍትን፣ የመጽሐፈ ኢያሱንና የመጽሐፈ መሳፍንትን ንባብና ትርጓሜ ያስተምራል።
  • ይህ ትምህርት ከመጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ እስከ መጽሐፈ አስቴር ድረስ ያሉትን መጻሕፍት ንባብና ትርጓሜ ያስተምራል።
  • በዚህ ትምህርት ተማሪዎች የቅኔ መጻሕፍት በመባል የሚጠሩትን መጻሕፍት ንባብና ትርጓሜ ይማራሉ (እነሱም-መጽሐፈ ኢዮብ፣ መጽሐፈ ምሳሌ፣ መክብብ፣ መኃልዬ መኃልይና የመዝሙር መጻሕፍት ናቸው።)
  • በዚህ ትምህርት ተማሪዎች የዐበይትና ደቂቀ ነቢያትን መጻሕፍት ንባብና ትርጓሜ ይማራሉ።
  • በዚህ ትምህርት የማቴዎስ ሉቃስ ማርቆስና የዮሐንስ ወንጌል መጻሕፍትንና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን ንባብን ትርጓሜ ይማራሉ።
  • በዚህ ትምህርት እግዚአብሔር በሐዋርያው ጳውሎስ በኩል ያጻፋቸውን መልእክቶች ንባብና ትርጓሜ ይማራሉ።
  • በዚህ ኮርስ ተማሪዎች የሐዋርያው ዮሐንስን ሦስት መልእክቶች፣ የሐዋርያው ጴጥሮስን ሁለት መልእክቶች፣ የያዕቆብና የይሁዳን መልእክቶችና የዮሐንስ ራዕይን ንባብና ትርጓሜ ይማራሉ።
  • ይህንን ትምህርት የሚማሩ ተማሪዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር አሐዱ ሥሉስነት የሚያስተምረውን በየዘመኑ በክርስቲያን አባቶች የተደረጉ ጉባኤዎችን በመዳሰስና ከታሪክ ጋር በማጣቀስ ይማራሉ። የእግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድና፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን መለኮትነት፣ አንድነትና ልዩነት በጥልቀት ይገነዘባሉ።
  • ይህ ኮርስ የሰውን ፍጥረት ምንነትና ማንነት እንዲሁም የኃጢአትን ባሕርይና ከእነዚህ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጉዳዮችን ያስተምራል።
  • ይህ ትምህርት የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቅበትንና ከዘለዓለም ሞት የሚድንበትን መንገድ በተመለከተ የሚነሱ አሳቦችን እየቃኘ ተማሪዎች ስለሚያምኑት እምነት ግልጽ የሆነ አቋም እንዲኖራቸው ያስችላቸዋል። ስለ ዳግም መወለድ፣ የኃጢአት ሥርየት እንዲሁም ከዳኑ በኋላ ያፈገፈጉ ስለሚኖራቸው ዕጣ ፈንታ፣ የወንጌልን የምሥራች ሳይሰሙ ስለሞቱና ስለመዳን ለመስማት አካላዊ ብቃት ስለሌላቸው ሰዎች ጉዳይ ጠለቅ ያለ ውይይት ይደረጋል።
  • ይህ ትምህርት የሥላሴ ሁለተኛ አካል የሆነውን የእግዚአብሔር ወልድን ማንነትና ምንነት በጥልቀት ያስተምራል። ተማሪዎች ከቅድመ ፍጥረት ጀምሮ ከዳግም ምጽአት በኋላ ስላለው የክርስቶስ ኢየሱስ ማንነት ይማራሉ። ፍጹም አምላክነቱንና ፍጹም ሰውነቱን በተመለከተ የሚነሱ ጥያቄዎችን በማንሳት ተማሪዎች ይወያያሉ። በታሪክ ውስጥ መለኮታዊና ሰዋዊ ባሕርዩን በተመለከተ አባቶች ተነጋግረው ውሳኔ ያሳለፉባቸውን ጉባኤዎች በነቂስ ይመለከታሉ።

መሓሪ የትምህርት አገልግሎት ዓላማው የሥነመለኮት ትምህርቶችን በአማርኛ ማስተማር ነው። በጠቅላላው ሰላሳ አንድ ትምህርቶችን የምናስተምር ሲሆን ተማሪዎች በቅደም ተከተል እንደቀረበው ከእነዚህ ትምህርቶች በአንዱ ይመዘገባሉ፡፡ ነገር ግን ሁሉም ተማሪዎች ሌሎችን ትምህርቶች ለመማር ከመመዝገባቸው በፊት የመጀመሪያዎቹን ሦስት መሠረታዊ ትምህርቶች መማር ይኖርባቸዋል፡፡ ለመመዝገብ የአንድ ጊዜ ምዝገባ ክፍያ $25 እንዲሁም ለእያንዳንዱ ኮርስ $50 እናስከፍላለን። ከአሜሪካ ካናዳና አውሮጳ ውጭ የምትኖሩ ከሆነ ጻፉልንና በስኮላርሺፕ የምትማሩበትን ሁኔታ እናመቻቻለን። ተማሪዎችን ስፖንሰር ለማድረግ ለምትፈልጉ ትምህርቱን ለመማር የተሰናዱ ተማሪዎች ስላሉን በእኛ በኩል ልታገኙዋቸው ትችላላችሁ። ተመዝግበው ትምህርት ለመጀመር ከፈለጉ በዚህ የኢሜይል አድራሻ ያግኙን MYWONGEL@YAHOO.COM

Skip Calendar

Calendar

Sun Mon Tue Wed Thu Fri Sat
      1 2 3 Today Saturday, 4 September 4
5 6 7 8 9 10 11
12 13 14 15 16 17 18
19 20 21 22 23 24 25
26 27 28 29 30